ስለ እኛ

ህይወትን ማጎልበት

የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን (ኢሲኤ) በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ውስጥ ያለውን የመቆጣጠር፣ የማሳለጥ እና አቅምን ለማሳደግ የሚሰራ የመንግስት ድርጅት ነው። ተልእኮው ተወዳዳሪ ኢንዱስትሪን የሚያበረታታ የቁጥጥር አገልግሎቶችን መስጠት፣ ፕሮጀክቶችን በወቅቱ፣ በበጀት ውስጥ እና በተቀመጡት ደረጃዎች መሰረት መፈፀምን ማረጋገጥ ሲሆን ሁሉም የአካባቢ እና ማህበራዊ ደህንነትን ከግምት ውስጥ በማስገባት ነው።
ራዕይ

በ2022 በተጠናከረ የቁጥጥር ስርዓት የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው በአፍሪካ ተወዳዳሪ ሆኖ ማየት!” Vision: To See Regulated & Most Competitive Construction Industry in Africa By 2030!

የኮንስትራክሽን ሥራዎች የአከባቢን እና የዜጎችን ጤንነትና ደህንነት የጠበቁና ምቹ መሆናቸውን በተቀመጡ ሕጎች፣ኮዶች እና ደረጃዎች መሠረት መከናወናቸውን የማረጋገጥ ሒደትን የሚመላክት ነው፡፡

ጠንካራ የቁጥጥር ስርዓት በመፍጠር እና ተፈጻሚነቱን በመረጋገጥ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ከሀገር ውስጥ ገበያ ተሻግሮ በጊዜ፣በጥራት እና በወጪ ቆጣቢነት በአፍሪካ ተወዳዳሪ በመሆን የውጭ ምንዛሪ የማምጣት አቅም እንዲኖረው ማስቻልን የሚያመለክት ነው፡፡

የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የግንባታ ፕሮጀክቶች በተገቢው ወጪ፣ጊዜ ጥራት መፈጸሙን እንዲሁም የዜጎችን፣የአካባቢ ደህንነትንና ጤንነትን መጠበቁን በማረጋገጥ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ ነው፡፡
ልህቀት፣ የቡድን ስራ፣ ግልጽኝነት፣ ምሉዕነት፣ ቁርጠኝነት፣ ተጠያቂነት፣ ዘላቂነት